ብርሃን ባንክ በወላይታ ሶዶ ከተማ በአይነቱ ልዩ የሆነውን የተማሪዎችን የክፍያ መተግበርያ ዘዴ (school pay)  አስተዋወቀ

   ብርሃን ባንክ በወላይታ ሶዶ  ከተማ የባንኩ ከፍተኛ የሰራ ኃላፊዎች እና የክልሉ ት/ቢሮ በተገኙበት  ቅዳሜ ህዳር 10 ቀን 2015 ዓ.ም  

   በዓይነቱ ልዩ የሆነውን  የተማሪዎች የክፍያ መተግበርያ ዘዴ (School pay )  በያቆብ ሆቴል ከ60 በላይ ለሚሆኑ ት /ቤቶች አስተዋወቀ ፡፡

   በዚህ ፕሮግራም ላይ  ከፍተኛ የባንኩ የስራ አመራሮች እና የክልሉ የትህምህርት ቢሮ ሀላፊዎች  የተገኙ ሲሆን የተማሪዎችን  

   የክፍያ መተግበርያ (school pay ) ዘዴ በባንኩ የዲጅታል እና የፋይናሻል ዳይሬክትር በሆኑት  በአቶ ፈየራ  ኤጃታ

   ከት/ቤትች እና ከክልሉ ት/ቢሮ  ለመጡ  ተሳታፊዎች ገላጻ ያደረጉ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪም ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች  ምላሽ ተሰጥቷል፡፡                      

በዚህ በመቀጠል በክልሉ ከ1900 በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ ያ ለው የቤዛኤል ት/ቤት የፋይናስ ሀላፊ የሆኑት አቶ ኤፍርኤም መንግስቱ  ብርሃን ባንክ በክልሉ   እያስተዋወቀ ያለው የተማሪዎች ክፍያ መተግበርያ ዘዴ በት/ቤቱ ያለውን የክፍያ ዘዴ ያዘመነ ከመሆኑ መተጨማሪ ለወላጆች እና  ለት/ቤቱ አሰራር ላይ ከፍተኛ አገዛ እንዳደረገ ገለጻዋል ፡፡

አያይዘውም የክልሉ የት/ም/ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ታደሰ ኩማ በማጠቃለያ ንግግራቸው እንደገለጹት ብርሃን ባንክ የተማሪዎች የክፍያ ዘዴ በጣም ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመጠቀም ት/ቤቶችን እና ለወላጆች በቀላሉ ከተማሪዎች የክፍያ ዘዴ ከመፈጸም በተጨማሪ አጠቃላይ የት/ቤቶች እና ወላጆች ግንኙኘትን ያቀራረበ ቴከኖሎጂ ነው ብለዋል፡፡