ብርሃን ባንክ የፖስ ማሽን ስርጭትን ለማሳደግ የሚያስችል ስምምነት ከሳንቲምፔይ ጋር ተፈራረመ!

ብርሃን ባንክ ከሳንቲምፔይ ፋይናንሺያል ሶሉሺን ጋር የነበረዉን አጋርነት በማስፋት የፖስ ስርጭትን ለማሳደግ እና ወደ ደንበኞች በይበልጥ ለመቅረብ የሚያስችል የፓስ አቅርቦት ስምምነት መፈራረሙን ስንገልፅ በደስታ ነው፡፡

በፖስ ማሽን አቅርቦት ዘርፍ የተጀመረው ስትራቴጂክ አጋርነት የኢትዮጵያን የዲጂታል እድገት ለማፋጠን እና የፖስ ስርጭትን በማሻሻል የባንኩን ደንበኞች እና የንግድ ማህበረሰቡን የግዢ እና የሽያጭ ስርዓቱን ሊያቀል የሚችል ትልቅ እርምጃ ሲሆን የዲጂታል ክፍያዎችን ተደራሽነት ለማስፋት እና የኢኮኖሚ እድገትን ለማበረታታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለዉ።
የፊርማ ስነስርዓቱ የብርሃን ባንክ ቺፍ ዲጂታል ባንኪንግ እና ስቴት ማኔጅመንት ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ቤተልሔም ጌታቸው እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የሳንቲምፔይ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ትንሳኤ ደሳለኝ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተከናውኗል፡፡