Berhan Bank አገር አቀፍ ግልፅ ጨረታ
- ብርሃን ባንክ በ2015 በጀት ዓመት የሚውሉ ከዚህ በታች በሰንጠርዥ የተዘረዘሩትን የተለያዮ የቢሮ ፈርኒቸሮች ግዥ ለማከናውን በዘርፉ የተሰማሩ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም
ምድብ ቁጥር | ዓይነት | ብዛት | የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና መጠን | የጨረታ መዝጊያ ቀን እና ሰዓት | የጨረታ ቁጥር |
I | የተለያዮ የቢሮ ጠረጳዛዎች | በብዛት | ዝርዝር የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና መጠን በጨረታ ሰነዱ ላይ ተጠቅሷል፡፡ | 17/12/2014 ዓ.ም በ4:00 ሰዓት | ብባ/ግጨ/ፈ/2022/23/10 |
II | የተለያዮ የቢሮ ወንበሮች | በብዛት | 17/12/2014 ዓ.ም በ4:00 ሰዓት | ብባ/ግጨ/ፈ/2022/23/11 | |
III | የባንክ ካውንተር | በብዛት | 17/12/2014 ዓ.ም በ8:00 ሰዓት | ብባ/ግጨ/ፈ/2022/23/12 | |
IV | የፋይል ማስቀመጫ ካዝና (Filing Cabinet) እና የብረት መደረደሪያ (Dixon Shelf) | በብዛት | 17/12/2014 ዓ.ም በ8:00 ሰዓት | ብባ/ግጨ/ፈ/2022/23/13 |
- ተጫራቾች ለዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ! የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ የምስክር ወረቀት እና የታክስ ከፋይነት የምስክር ወረቀት የሚያቀርቡ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በማንኛዉም የብርሃን ባንክ ቅርንጫፍ ክፍያ ፈፅመዉ ደረሰኙን በማቅረብ፣ የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ከሚገኝበት ቦሌ ብራስ ሆስፒታል ፊት ለፊት ከሚገኘዉ ወመሳድኮ ህንፃ 2ተኛ ፎቅ ከፋሲሊቲ አስተዳደር መምሪያ ቢሮ ለጨረታዉ የተዘጋጀዉን ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የቴክኒክ ሰነድ እና የዋጋ ሰነድ አንድ በዋና እና አንድ በኮፒ በተለያዮ ፓስታ ማቅረብ እንዲሁም ናሙና ማያያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን ከላይ በሰንጠረዥ በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት ድረስ የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ከሚገኝበት ቦሌ ብራስ ሆስፒታል ፊት ለፊት ከሚገኘዉ ወመሳድኮ ህንፃ 2ተኛ ፎቅ ፋሲሊቲ አስተዳደር መምሪያ ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማሰገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው ከላይ በሰንጠረዥ በእያዳንዱ ምድብ በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓትከ30 ደቂቃ በኋላ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ከሚገኝበት ቦሌ ብራስ ሆስፒታል ፊት ለፊት ከሚገኘዉ ወመሳድኮ ህንፃ 2ተኛ ፎቅ ፋሲሊቲ አስተዳደር መምሪያ ቢሮ ይከፈታል፡፡
- ባንኩ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታዉን በከፊል ወይም ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፡፡
ብርሃን ባንክ አ.ማ.
ፋሲሊቲ አስተዳደር መምሪያ
ሰልክ ቁጥር 011 663 2097/011 650 7422